አንድ ሸማች በሻጩ ላይ የይገባኛል ጥያቄን ክስ በሀሻሎም ፍርድ ቤት በኩል ማቅረብ ይችላል። ሆኖም ግን ይህ ክስ በጠበቃ የታገዘ መሆን አለበት ። ሌሎች ለተጠቃሚዎች የሚዳኙ ፍርድ ቤቶች የአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤትና የተለያዩ የሚያገላግሉ አካላትም ይኖራሉ ።
ከ 1/1/24 ጀምሮ አንድ ሸማች የይገባኛል ጥያቄው መጠን ከ 37,700 ሸቄል የማይበልጥ ከሆነ በይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ ይችላል ። ይህን ክስ ከማቅረቡ በፊት የአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት ጽሕፈት ቤቱን ወይም የሸማቾች ድርጅቶችን ማማከር ይመከራል ።
ለአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄዎች ፍርድ ቤት የተሰጡት ስልጣኖች
የአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት ሸማቹ ባቀረበው ብቁ የሆነ ማስረጃ ያለው ከሆነ ፤ ለሻጩ ፤ የተቀበለውን ገንዘብ እንዲመልስ ፤ ምርቱን በሌላ ምርት እንዲተካ ወይም እንዲጠግንና ግብይቱን እንዲሰርዝ ብሎ የመፍረድ መብት አለው ።
ያለ ጠበቃ ውክልና የሚደረግ ፍርድ
በትንሽ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት ውስጥ ያሉ ወገኖች ጠበቆችን እንዲጠቀሙ አይፈቀድላቸውም ፤ ነገር ግን በተለያዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ፍርድ ቤቱ ይህን እንዲያደርጉ ሊፈቅድላቸው ይችላል ።
ክሱ የሚቀርበው የት ነው ?
በተጠቃሚውና በሻጩ መካከል በተደረገው ስምምነት መሰረት ክሱ መቅረብ ያለበት ቦታ ቢመደብም ቅሉ፤ ሸማቹ ክሱን ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት ቦታዎች በአንዱ ለአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል ።
በኢንተርኔት ላይ በማስታወቂያ ወይም በንግድ ምክንያት የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳበት ጊዜ የይገባኛል ጥያቄው የሚቀርበው ችሎቱ የከሳሹ ወይም የተከሳሹ የመኖሪያ ቦታ ወይም የንግድ ቦታ ብቻ ነው ።
የግብር ክፍያ
ለአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት የይገባኛል ጥያቄ ያቀረበ ሸማች ፤ በሕግ መሰረት የግብር ክፍያ መክፈል አለበት ።
የይገባኛል ክስ ጥያቄ መግለጫ ፤ የክሱ መከላከያ መግለጫና የፍርድ ቤት ሂደቶች
ሸማቹ ባቀረበው የይገባኛል ጥያቄ መግለጫ ውስጥ የእርሱን መግለጫ ዝርዝር ሁኔታዎችና የተከሳሹን ፤ ስም ፤ የመታዎቂያ / የመለያ ቁጥር (የግል የመታወቂያ ቁጥር ወይም የድርጅቱ ቁጥር) ፤ አድራሻና የመገናኛ ዘዴዎች ዝርዝሮችን መግለጽ አለበት ። በንግድ ሥራ ላይ በተመሰረተው ክስ ውስጥ ፤ በብዙ ጉዳዮች ላይ የንግዱን ባለቤትና / ወይም ተወካዩን ፤ እንደ ተከሳሾች አድርጎ ጨምሮ ማቅረብ በጣም ጠቃሚ ነው። የይገባኛል ጥያቄውን በድርጅቱ ባለቤት ወይም በድርጅቱ ተወካይ ላይ ስለማቅረብ ጥርጣሬ ካለ ምክር ለማግኘት ወደ ሸማቾች ማሕበር በመደወል አስተባባሪዎችን ማነጋገር ይችላሉ ።
በደብዳቤው ላይ የይገባኛል ጥያቄ አቅራቢው ሸማች የተፈፀመውን ግብይት መግለጽ ፤ የተፈፀመበትን ቀንና ቦታ መግለጽ ፤ የገንዘብ ጥያቄ ከሆነ የገንዘብ ይገባኛል ጥያቄውን መጠን መግለጽና የተጠየቀውን የማግኘት መብት ያለው ለምን እንደሆነ ማስረዳት አለበት (ካሳ ፤ የምርት መተካት ፤ ግብይቱን መሰረዝ ፤ ወ.ዘ.ተ.) ። ተከሳሹ በፍርድ ሂደቱ ላይ ሊተማመንባቸው የሚፈልጋቸው ሁሉም ሰነዶች በእጁ ውስጥ ካሉ የይገባኛል ጥያቄ መግለጫው ጋር በማያያዝ ለፍርድ ቤቱ መቅረብ አለባቸው ።
የይገባኛል ጥያቄው ከቀረበ በኋላ ተከሳሹ የይገባኛል ጥያቄው ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ የመከላከያ መግለጫ እንዲያቀርብና በፍርድ ቤቱ ጽሕፈት ቤት በተቀጠረበት ቀን ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ይታዘዛል ።
ፍርድ ቤቱ የተከራካሪ ወገኖች ማስረጃ የሚቀርብበትን ቅደም ተከተል ይወስናል። ክርክሩን በንቃት በማብራራት የተፈጠረውን አለመግባባት ማጣራት ይጀምራል ።
ፍርድ ቤቱ ከችሎቱ በኋላ የይገባኛል ጥያቄውን ይወስናል ፤ አንዳንድ ጊዜ ለሁለቱም ወገኖች ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ሐሳብ ያቀርባል ፤ ይህ ስምምነት የፍርድ ውሳኔ ውጤትነት ይኖረዋል ፤ ፍርድ ቤቱ ፍርዱን በአጭሩ ማስረዳት አለበት ፤ ፍርዱ በሚሰጥበት ጊዜ ሁለቱም ወገኖች በተጠቀሰው የፍርድ ቤት ውሳኔ መሰረት መሥራት አለባቸው ።
ይግባኝ የማቅረብ ፍቃድ
በአነስተኛ የይገባኛል ጥያቄ ፍርድ ቤት፣ ፍርድ ላይ ይግባኝ ለማለት የሚፈልግ ወገን በክልሉ ወረዳ ፍርድ ቤት በመሄድ ማመልከትና ይግባኝ ለማለት የፍቃድ ጥያቄ ማቅረብ ይችላል ። ይህንም ማድረግ የሚችለው የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከተወሰነና የውሳኔው ደብዳቤ ከእጁ ከገባ በ15 ቀናት ውስጥ ነው ።
በዚህ የመምሪያ መጽሔት ውስጥ የቀረበው መረጃ አጠቃላይ መረጃ ብቻ ነው ፤ ግን ሕጋዊ ምክርን የሚተካ አይደለም እና ያለ ተገቢ ምክር ብቻዉን መታመን የለበትም.
ይህ መምሪያ ሰኔ ወር 2023 ዓ.ም. ያለውን መረጃ በሕጉ እና ደንቡ ላይ በመመርኮዝ ተሻሽሏል ።
አስገዳጅ የሚሆነው የሕጉ እና የደንቡ ጽሑፍ ነው።