በአንድ ወገን ብቻ የተዘጋጁ ስምምነቶች

በአንድ ወገን ብቻ የተዘጋጁ ስምምነቶች

በአንድ ጎን ብቻ የተዘጋጁ ዉሎች ማለት “ቁጥራቸው ባልታወቀ ሰዎች ወይም በማንነታቸው በማይታወቁ ሰዎች መካከል ለሚደረጉት ብዙ ውሎች ፣ በአንድ ተዋዋይ ወገን ውሉ በሙሉ ወይም በከፊል የተወሰነው የውል ሰነድ ነው " ይህ ሻጭ ለሸማቹ ውል የሚያቀርብበት ሁኔታ አስቀድሞ በሻጩ በተወሰነው ስምምነት ዓይነት (ይህ ሁኔታ ጥቅም ላይ የሚውልበት ሁኔታ ለምሳሌ በግንኙነቶች መስክ ከትላልቅ ኩባንያዎች ጋር ውል ሲደረግ ፤ የባንክ አገልግሎት፣ የኋይል አቅርቦት) ጉልበት የሚሰጠው ሰነድ ማለት ነው ። የዚህ ዓይነት ውልን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች የተመሰረቱት በአንድ ጎን ብቻ የተዘጋጁ ዉሎችን በሚመለከተው ሕግ መሰረት ነው። ሕጉም የተደነገገው በ 1982 ዓ.ም ሲሆን፣ ዓላማው ሸማቾችን ከአደጋ ከሚያስከትሉ ሁኔታዎች ለመጠበቅ ነው። ይህም ሲባል በፓርቲዎች መካከል ባለው የመረጃና የስልጣን ክፍተት ምክንያት የሸማቹ ህብረተሰብ ለችግር መዳረጉን በመረዳት ነው ።

መድሏዊ ድርጊቶች ማለት ፤ ሸማቾችን የሚጎዳ ወይም ለነጋዴው የኢ-ፍትሃዊ ጥቅም የሚያደላና ሸማች የሚደርሱትን ጥቅሞች እንዲያጣ የሚያደርግ ሁኔታ ነው ።

ከዚህ በታች በሕግ የተደነገጉ ሁኔታዎች መድሎ ናቸው ተብሎ የሚታመኑ አንዳንድ ምሳሌዎችን ያቀርባሉ ።

  1. አገልግሎት አቅራቢውን በሕግ ከተጣለበት ተጠያቂነት፣ነፃ የሚያደርገው፣ ወይም ያለምክንያት በስምምነቱ መሰረት የጣልበትን ኋላፊነት ላለመወጣት የሚያደርገው ሁኔታ ።
  2. የሻጩ ሁኔታ የውሉን አፈጻጸም ለመሰረዝ፣ ለማገድ ወይም ለሌላ ጊዜ ለማስተላለፍ ወይም በውሉ መሰረት አስፈላጊ የሆኑትን ድርጊቶች የመቀየር ሕጋዊ ያልሆነ መብትን ለሻጩ የሚሰጠው ።
  3. ሻጩ ኃላፊነቱን ለሶስተኛ ወገን የማስተላልፍ መብት የሚሰጥበት ሁኔታ
  4. ውሉ ከተጠናቀቀ በኋላ አቅራቢው በደንበኛው ላይ የሚጣለውን ዋጋ ወይም ሌላ ጉልህ ክሶች የመወሰን ወይም የመቀየር መብት የሚሰጠው ሁኔታ (ከአቅራቢው ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ሁኔታዎች ምክንያት ለውጥ ካልሆነ በስተቀር) ።
  5. በውሉ መሠረት የአንድን ዋጋ ወይም ሌላ ክፍያ ከአንዳንድ ማመዛዘኛ ንግዶች ጋር ማገናኘት የሚወስንበት ሁኔታ ፤ ስለዚህም የማመዛዘኛ ንግዶች መቀነስ ወይም መጨመር ለደንበኛው አይጠቅምም ።

ፍርድ ቤቱና የፍርድ መስጫ ተቋሞች ለሚደረጉ ዉሎች፣ ልዩና በአንድ ወጥ ውል ውስጥ ያሉ መጥፎ ሁኔታዎችን ለመሰረዝ ወይም ጉዳት እንዳይደርስባቸው እንዲቀይሩ ተፈቅዶላቸዋል ።

 

 

በዚህ የመምሪያ መጽሔት ውስጥ የቀረበው መረጃ አጠቃላይ መረጃ ብቻ ነው ፤ ግን ሕጋዊ ምክርን የሚተካ አይደለም እና ያለ ተገቢ ምክር ብቻዉን መታመን የለበትም.
ይህ መምሪያ ሰኔ ወር 2023 ዓ.ም. ያለውን መረጃ በሕጉ እና ደንቡ ላይ በመመርኮዝ ተሻሽሏል ።
አስገዳጅ የሚሆነው የሕጉ እና የደንቡ ጽሑፍ ነው።