በሸማቾች መብት ጥበቃ ሕግ መሠረት የሚከፈሉ የማካካሻ ክፍያዎች ፤ ለምሳሌ

በሸማቾች መብት ጥበቃ ሕግ መሠረት የሚከፈሉ የማካካሻ ክፍያዎች ፤ ለምሳሌ

በሸማቹና በነጋዴው መካከል የግብይት ውል ከተደረገና ግብይቱ ከተፈጸመና ሻጩ ይህን የግብይት ውል ካፈረሰ፣ በሕጉ መሰረት ሻጩ ለሸማቹ ካሳ መክፈል አለበት ።ለምሳሌ፣ ሸማቹም የሚደርሰውን ካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብት አለው፣ ለምሳሌ እነዚህ የካሳ ዓይነቶች ከተፈጠረው የዕቃ መበላሸት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም። ይህም ማለት ይህን ካሳ ለማግኘት ሸማቹ አስፈላጊውን ማረጋገጫ የማምጣት ኃላፊነቱ በእርሱ ላይ ይጣላል። ግን ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰበት ማረጋገጫ ማቅረብ አይተበቅበትም።

ሕጉ ይህን ይወስናል፣የሚከፈለውን የምሳሌ ማካካሻ መጠን ለመወሰን የሕጉን ድንጋጌዎች በመጣሱ ምክንያት በተጠቃሚው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ግምት ውስጥ ማስገባት እንደማይችል፣ ነገር ግን ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚችል፤

  1. የሕግ አጠባበቅና ሕጉ እንዳይጣስ የሚደረጉ መከላከያዎች
  2. ሸማቹ መብቱን እንዲያስከብር ማበረታታት
  3. የሕግ ጥሰቱ ክብደት የገንዘቡ ወሰንና ምክንያቶቹ
  4. የተፈጸመበት የግብይት ገንዘብ ብዛትና የደረሰው የሕግ ጥሰት
  5. የሻጩ የንግድ የገንዘብ መጠን
  6. በጥሰቱ ምክንያት በሸማቾች ጥበቃ ሕግ ውስጥ የተቀመጠው የገንዘብ ቅጣት መጠን፣

ስለሆነም ፍርድ ቤቱ የሚወስነው የምሳሌ ማካካሻ የገንዘብ ብዛት አንዳንድ ጊዜ ከደረሰው ጉዳት የበለጠ ሊሆን ይችላል ፤ ይህም ማለት ከላይ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች ግምት ውስጥ በማስገባት ፍርዱን ሊሰጥ ስለሚችል ነው ።

የሸማቾችን ጥበቃ ሕግን የሚጥስ ሁሉ ለሸማቹ ለምሳሌ፣ ካሳዎችን ሁል ጊዜም እንደማይቀበሉ መብትም እንደሌላቸው ሕጉ በዝርዝር አስቀምጦታል ። ሆኖ ግን የሕጉ ክፍል 31 ላይ እንደተጠቀሰው አንድ ሸማች የምሳሌ ካሳ ሊጠይቅ የሚችልበትን ሁኔታዎች በዝርዝር አስቀምጧል

ከዚህ በታች ያሉት ዝርዝር ሁኔታዎች ደግሞ ፤ ፍርድ ቤት ለምሳሌ የሚከፈሉ ካሳዎች ከ 10,000 ሸቄል በላይ እንደማይፈርድ የሚያሳዩ ሁኔታዎች ናቸው ፤

  1. የሸማቾች የገዙትን ዕቃ የመመለስ ፖሊሲን ተግባር ላይ የማያውል ሻጭ ወይም ገዢው የገዛውን ዕቃ ለመመለስ የከፍለውን መልሶ አለመስጠት
  2. አንድ ሻጭ የገዥዎችን የዕቃ መመለስ ደንብ ተግባራዊ ሳያደርግና የሚያስፈልገውን የዕቃዎች መመለስ ደንብ ያላስታወቀ ፤ ሸማቹ በጠየቀው መሰረት ዋጋው ካልተከፈለው ።
  3. የተሸመቱ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቱን በተዋዋሉበት መሰረት ከቦታው ሳያደርስ የቀረ ሻጭ
  4. ምንም እንኳን ሸማቹ ግብይቱ ካለቀ በኋላ የመክፈሉን ሂደት እንዲያቆም ቢጠይቅም ሻጩ ግን ሸማቹን ክፍያ ማስከፈል የቀጠለ ከሆነ።
  5. በሕጉ መሠረት ግብይቱ የሚቋረጥበትን ቀን ለተጠቃሚው ሳያሳውቅ ፤ ግብይቱ ከተቋረጠበት ቀን በኋላ በተወሰነ ጊዜ ግብይት ውስጥ ሻጩ በክፍያ ማስገደዱን የቀጠለ ከሆነ
  6. የስረዛ ማስታወቂያ ቢደርሰውም በመካሄድ ላይ ባለ ግብይት ሸማቹን በክፍያ ማስከፈል የቀጠለ ሻጭ ።
  7. በመካሄድ ላይ ባለው ግብይት ለተጠቃሚው ከመጠን በላይ ዕዳ ያለበትና ለተጠቃሚው ያልመለሰ ሻጭ ፤ ገዥው በጠየቀው መሰረት ፤ በሕጋዊ መንገድ ሊከፈለው የሚገባውን የገንዘብ መጠን ሻጩ ካልከፈ ።
  8. የክፍያ ዘዴዎችንና የተከለከሉ ክፍያዎችን በተመለከተ የተለያዩ ድንጋጌዎችን የጣሰ ሻጭ
  9. ሸማቹ በሕጋዊ መንገድ ቢሰርዘውም የሽያጭ ግብይቱን ያልሰረዘ ሻጭና በስምምነቱ መሰረት የተቀበለውን ዋጋ ለተጠቃሚው ያልመለሰ ከሆነ
  10. ሸማቹ በሕጋዊ መንገድ ግብይቱን ቢሰርዘውም ወይም የዝውውሩን የዋጋውን ክፍል ለተጠቃሚው ያልመለሰ ቢሆንም ለዕረፍት ክፍል ግዢ ወይም የዕርቀት የሽያጭ ግብይትን ያልሰረዘ አከፋፋይ ።
  11. ምንም እንኳን ሸማቹ በሕጋዊ መንገድ ግብይቱን ቢሰርዘውም ወይም የዋጋውን ክፍል ለተጠቃሚው ባይመልስም የሕክምና አገልግሎቶችን በሚመለከት እየተካሄደ ያለውን ግብይት ያልሰረዘ አከፋፋይ ።
  12. ሻጩ ቢጠይቅም ሻጩ በምርቱ ላይ ከሚታየው ዋጋ በላይ ገዚውን ካስከፈለ
  13. ሸማቹ የሚገዛውን ዕቃ ወይም የአገልግሎት ዋጋን በእስራኤል ምንዛሪ ገንዘብ እንዲከፍል ያልፈቀደ ሻጭ ።
  14. በሸማቾች ደኋንነት ጥበቃ ሕግ መሰረት በማድረግ አንድ ሸማች ቢያንስ 150 ሽቄል በሆነ ወጪ የኤሌክትሪክ ፤ የኤሌክትሮኒክስ ምርት ወይም የጋዝ ምርት ለገዛ ሸማች የዋስትና ምስክር ወረቀት ወይም የአንድ ዓመት የተለጣፊ ዋስትና ያልሰጠ ሻጭ
  15. በመጀመሪያው ዓመት የዋስትና ጊዜ ውስጥ በተጠቃሚው ጥያቄ መሰረት ቢያንስ 150 ሼቄል አውጥቶ የግዛው የኤሌክትሪክ ምርት የኤሌክትሮኒክስ ምርት ወይም በጋዝ ምርት የደረሰበትን ጉድለት የማያስተካክል ሻጭ ።

ምሳሌ፣ልዩ በሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ቤቱ እስከ 50,000 ሸቄል የሚደርስ ካሳ ሊፈርድበት ይችላል፣

 

  1. ተደጋጋሚ ስምምነትን አለማክበር - በተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሰበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሻጩ የሸማቾችን ጥበቃ ሕግ ጥሶ ከተገኘ
  2. ማስታወቂያ ወይም ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ ነጋዴው በሕጉ መሰረት ከፈጸመው ድርጊት እንዲታቀብ ወይም ይህን መሰል ወንጀል ለመከላከል አስፈላጊ የሆነውን ማንኛውንም እርምጃ እንዲወስድ፣ ወይም በማስታወቂያው ወይም በትዕዛዙ ውስጥ ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ የተፈጸመ ስምምነትን አለማክበር፣ ወይም የድንጋጌው ጊዜ ያለፈበት፣ (ከእነዚህ ሁሉ ወደ ኋላ የተደነገገውን በመከተል) ።
  3. በጣም አደገኛ በሆኑ ሰበቦች ስምምነቱን ስለመጣስ - ከዚህ በታች ካሉት ዝርዝር ምክንያቶች ውስጥ በአንዱ፣

ሀ. በተለይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ሸማቾች የሚመለከት ጥሰት

ለ. በብዙ ተጠቃሚ ቡድኖች ላይ ወይም በአንድ ገዥ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ጥሰት ። ሐ. ሻጩ ባደረገው የውል ጥሰት ምክንያት ትልቅ ትርፍ ወይም ጥቅም ካገኘ ፣

መ. የስምምነት ጥሰቱ የተደረገው ለአረጋውያን ፤ አቅመ ደካሞች ወይም ለአካለ መጠን ላልደረሱ ልጆች ወይም የአእምሮ ሕሙማን ወይም የአካል ደካሞች ወይም ግብይቱ ለማካሄድ በቂ ቋንቋ ለማያውቁ የተጠቃሚዎች ከሆነ ነው

ሰ. የስምምነት ጥሰቱ ከማታለል ጋር የተያያዘ ሲሆን አስረጂው የሚያውቀውን ዕውነት ያልሆነ ነገር ዕውነት ነው ብሎ ካሳመነ ነው ።

 

ለምሳሌ፣ ካሳ የማግኘት መብት የተገልጋዩን የሚደርሱት ሌላ መብቶች ላይ አይቀንስም ። ለምሳሌ ሸማቹ ከሚደርሰው ካሳ በላይ በሆነ መጠን የገንዘብ ጉዳት ከደረሰበት ፤ ለምሳሌ ለእነዚህ ሁኔታዎች ካሳ የመጠየቅ መብት ይኖረዋል ፤ ነገር ግን በዚህ ሁኔታ የደረሰበትን ጉዳት መጠን ማረጋገጥ ይኖርበታል ። በተጨማሪም ማንኛውንም መደበኛ ክስ ይጨምራል ።

ሸማቹ ፣ለምሳሌ፣ ለጉዳት ካሳ ያለው የይገባኛል ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው ሸማቹ ለሻጩ በላከው ወይም ላቀረበው ጥያቄ ምላሽ ያላገኘውን የጽሁፍ ጥያቄ (ለዚህ ዓላማ - በኤሌክትሮኒክስ ግንኙነት መላክ) ብቻ መሆኑን አቅርቦ መስጠት አስፈላጊ ነው ። በሕጉ ውስጥ እንደተገለጹት አንዳንድ ሁኔታዎች ሸማቹ በሕጉ ላይ እንደተገለጠው ግብይቱን ከሰረዙው በቂ ነው ሸማቹ እንደዚህ ዓይነት ማስታወቂያ እንዲልክ አይገደድም

 

 

በዚህ የመምሪያ መጽሔት ውስጥ የቀረበው መረጃ አጠቃላይ መረጃ ብቻ ነው ፤ ግን ሕጋዊ ምክርን የሚተካ አይደለም እና ያለ ተገቢ ምክር ብቻዉን መታመን የለበትም.
ይህ መምሪያ ሰኔ ወር 2023 ዓ.ም. ያለውን መረጃ በሕጉ እና ደንቡ ላይ በመመርኮዝ ተሻሽሏል ።
አስገዳጅ የሚሆነው የሕጉ እና የደንቡ ጽሑፍ ነው።